16ኛው ዙር የይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ የውጭ ምንዛሬ ማበረታቻ ሽልማት ወጣ

47

 አዲስ አበባ ግንቦት 6/2011   16 ኛው  ዙር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ  የይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ የውጭ ምንዛሬ  ግኝት ማበረታቻ ዕጣ በዛሬው ዕለት ለባለድለኞች ይፋ ሆነ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቁጠባ ባህሉን በማሳደግ በአገሪቷ የፋይናንስ ስርዓት ውስጥ ከሚያበረክተው የላቀ ድርሻ ባሻገር የውጭ ምንዛሪ ለማሳደግም የይቀበሉ፣ ይመንዝሩ፣ ይሸለሙ መርሃ ግብር ዘርግቶ እየሰራበት ይገኛል።

ዛሬ በብሔራዊ ሎተሪ አዳራሽ ይፋ በሆነው 16ኛው ዙር ሽልማት መሰረትም አንደኛው የቤት  አውቶሞቢል የዕጣ ቁጥር  7299899  አሸናፊ ሲሆን  ይህም በባንኩ በፍቼ ቅርንጫ ወጥቷል።

በሁለተኛው ዕጣ ላይ ሁለት የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎችም  ለባለድለኞች የወጡ ሲሆን የአንደኛው ቁጥር የዕጣ ቁጥር 7355685  ብሔረ ጽጌ አካባቢ ቅርንጫፍ፣ ሁለተኛው የዕጣ ቁጥር  7301910 ጀሞ ቅርንጫፍ ደርሰዋል።

በተጨማሪም 16 ፍሪጆች፣ 64 ስማርት የሞባይል ቀፎዎች 3ኛና 4ኛ ዕጣ ሆነው ለባለዕድለኞች ወጥተዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ16ቱ  ዙር  ለባለድለኞች  ከ24 ሚሊዮን ብር በላይ  ወጪ ማድረጉን   በዕጣ አወጣጡ ወቅት ተገልጿል።

ከዚህም በተጫመሪ ባንኩ  አገራዊ የቁጠባ ባህልን ለማበረታት በይቆጥቡ ይሸለሙ  መርሃ - ግበር  ብዙ ዜጎችን  እንዲቆጥቡ ማስቻሉን  ከባንኩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም