አቶ ኡመር ሁሴን የኦዴፓ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሆነው ተመረጡ - ኢዜአ አማርኛ
አቶ ኡመር ሁሴን የኦዴፓ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሆነው ተመረጡ
112
መጋቢት 19/2011 የኦሮሚያ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባካሄደው ስብሰባ በዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ምትክ አቶ ኡመር ሁሴንን የኮሚቴው አባል አድርጎ መርጧል።
የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ(ኦዴፓ) ጽ/ቤት ሃላፊ ዶክተር አለሙ ስሜ በዚህ ጉዳይ ላይ ለሚዲያዎች ማብራሪያ መስጠታቸውን የኦሮሚያ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
በዚሁ መሰረት የኦዴፓ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴዎች፡-
- ዶክተር አቢይ አህመድ
- አቶ ለማ መገርሳ
- አቶ ኡመር ሁሴን
- ዶክተር አለሙ ስሜ
- አቶ ሽመልስ አብዲሳ
- አቶ አዲሱ አረጋ
- ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
- አቶ ፍቃዱ ተሰማ
- አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ መሆናቸው ተገልጿል።