የደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመረቀ - ኢዜአ አማርኛ
የደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመረቀ
128
ደብረ ብርሃን ካቲት 23/2011 ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክን በጋራ በይፋ መርቀዋል።
ፓርኩ በ1ሺ100 ሄክታር መሬት ስፋት ላይ የሚያርፍ ሲሆን ፤ ዛሬ ተመርቀው ወደ ስራ የገቡት ስምንት ሼዶች የተገነቡት በ70 ሄክታር ቦታ ላይ ያረፉ ናቸው።
ይሄው በመጀመሪያው የግንባታ ምዕራፍ 72 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ኢንዱስትሪ ፓርክ ፤ ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት እንደሚያመርት ታውቋል።
በቀጣይ የኢንዱስትሪ ፓርክ በግብርና ማቀነባበሪያ ላይ አተኩሮ እንደሚሰራ ከስፍራው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።