ዋሽንግተን ዩኒቨርሰቲ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር ሊሰሩ ነው

78
ህዳር 14/2011 ዋሽንግተን ዩኒቨርሰቲ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር  ተባብረው ሊሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቋሚ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ከሳ ተክለብርሃን ከዋሽንግተን ዩኒቨርስቲ የሚልጋርድ የቢዝነስ ትምህርት ቤት ኃላፊዎች ጋር ተባብረው በሚሰሩበት መንገዶች ላይ ምክክር ማድረጋቸውን  ተነግሯል፡፡ አምባሳደሩ  ከትምህርት ቤቱ ዲን ሃዋርድ ስሚዝ እና ሌሎች የተቋሙ ኃላፊዎች ጋር ነው በከፍተኛ የትምህርት መስክ ሊኖር በሚችል ትብብር ዙሪያ የተወያዩት፡፡ በውይይቱ ማጠናቀቂ በዋሽንግተን ዮኒቨርስቲ እና ሌሎች የአገራችን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሀከል ትስስር ለመፍጠር ከመግባባት መደረሱ ተጠቁሟል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መግለጫ ላይ እንደተጠቀሰው የሚልጋርድ የቢሰኮስ ትምህርት ቤት በአንደኛና በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚሰጥ ሲሆን የተመሰረተው እ.ኤ.አ. 1994 ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም