የአማራ ክልል ምክርቤት አዳዲስ ሹመቶችን አጸደቀ

96
ባህር ዳር ጥር 24/2011 የአማራ ክልል ምክርቤት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ለምክትል ርዕሰ መስተዳደርና ለቢሮ ሃላፊዎች አዳዲስ ሹመቶችን አጸደቀ። በክልሉ ርዕሰ-መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አቅራቢነት አቶ ላቀ አያሌውን ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር፣ አቶ ንጉሱ ጥላሁንን በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ በማድረግ ሹሟል። እንዲሁም አቶ መላኩ አለበል በምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ልማት ቢሮ ኃላፊ አድርጎ ሾሟ። ምክር ቤቱ ለሌሎች ኃላፊነቶችም የቀረበውን ሹመት መርምሮ አፅድቋል፡፡በዚህም መሰረት፦
  1. ዶክተር ቦሰና ተገኘ የግብርና ቢሮ ኃላፊ
  2. የቴክኒክ፣ ሙያና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ -አቶ ሻምበል ከበደ
  3. የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ -ወይዘሮ ብዙአየሁ ቢያዝን
  4. የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ መስሪያ ቤት- አቶ ፍርዴ ቸሩ
  5. የሰላም ግንባታና የህዝብ ደህንነት ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ -ብርጋዴር ጄነራል አሳምነው ጽጌ
  6. የሴቶች፣ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ -ወይዘሮ አስናቁ ድረስ
    1. የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ - ዶክተር ሙሉነሽ አበበ በማድረግ የሾመ ሲሆን 4 የጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ 5 የከፍተኛ ፍርድ ቤት፣6 የወረዳ ፍርድ ቤት ዳኞችን ሹመትም አጽድቋል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም