አምባሳደር ስለሺ በቀለ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር ተወያዩ - ኢዜአ አማርኛ
አምባሳደር ስለሺ በቀለ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር ተወያዩ
119
አዲስ አበባ (ኢዜአ) ጥር 24/2015 በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ የሰላም ስምምነቱን ትግበራ ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ከአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር መወያየታቸው ተገለጸ።
አምባሳደር ስለሺ ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ ጋር የሰላም ስምምነቱን ትግበራ እና ሂደት እንዲሁም የማህበራዊና ኢኮኖሚ ልማት ጨምሮ ሌሎችም ጉዳየች ላይ ያተኮረ ውይይት ማድረጋቸውን በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ አምባሳደር ማይክ ሀመር ጋርም መነጋገራቸውን አመልክተዋል።