የዳያስፖራ አደረጃጀቶች የእውቅና መርሐግብር ዛሬ ይካሄዳል - ኢዜአ አማርኛ
የዳያስፖራ አደረጃጀቶች የእውቅና መርሐግብር ዛሬ ይካሄዳል
262
አዲስ አበባ (ኢዜአ) ጥር 18/2015 ዳያስፖራው ለኢትዮጵያ እያደረገ ላለው ሁለንተናዊ ድጋፍ እና በጎ ተሳትፎ እውቅና የሚሰጥበት መርሐግብር ዛሬ ይካሄዳል።
በመርሐግብሩ ላይ ለሚካፈሉ አመራሮችና ተወካዮች የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሐመድ እንድሪስ እና ሌሎችም የስራ ኃላፊዎች አቀባበል እንዳደረጉላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
የእውቅና ስነ ስርዓቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የዳያስፖራ አባላት በተገኙበት እንደሚከናወን አመላክቷል።