በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትና ሌሎች መንግስታዊ ተቋማት ስም ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት በሚያጭበረብሩ ሰዎች ላይ እርምጃ እየተሰወሰደ ነው

239

አዲስ አበባ (ኢዜአ) ጥር 4/2015 የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትና ሌሎች መንግሥታዊ ተቋማት ስም ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት አባል ነን በማለት ኅብረተሰቡን እያጭበረበሩ በሚገኙ ግለሰቦች ላይ ጥብቅ ክትትል በማድረግ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መረጃ እንዳመለከተው፤ ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት የደኅንነትና የሌሎች መንግሥታዊ ተቋማት አባል ነን የሚሉ ግለሰቦችን በተመለከተ በተለያዩ መንገዶች ክትትል ሲደረግ ቆይቷል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህም በዚህ የማጭበርበሪያ ስልት የሚጠቀሙ አካላት ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ እርምጃ መውሰድ ተጀምሯል፡፡

ሰሞኑን በተደረጉ ጥብቅ ክትትሎችም

ምናልባት የ1 ሰው ምስል

ፈለቀ ዴብሳ ደማ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02፤

ምናልባት የ1 ሰው ምስል

አስፋው አዳማ ሙታ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01፤

ምናልባት የ1 ሰው እና '04/0150 የኢ.ፌ.ዴ.ፌ ብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት F.D.R.E, National Intelegensi & Security Service ሳምሶን ገነነ መንገሻ SAMSON GENENE MANGESHA የሚያበቃበት ቀን 14/06/2015 Expire Date Februry 21/2023 G.C' የሚል ጽሑፍ ምስል

ሳምሶን ገነነ መንገሻ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5፤

ምናልባት የ1 ሰው እና '08/0749 የኢፌዴ.ሪ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት F.D.R.E. National Intelligence & security ተስፋ ሀታው ገምቴሳ TESFA HATAWU GEMTESA የሚያበቃበት ቀን 02/06/2017 ዓ.ም Date of Expiry 09/02/2025' የሚል ጽሑፍ ምስል

ተስፋ ሀተው ገምቴሳ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳደር ሰበታ ክፍለ ከተማ፤

ምናልባት የ1 ሰው እና '01/0054 የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት F.D.R.E. National Intelligence Security Service GH ዮሰንበቀለ በቀለ ትክሳ YOSAN BEKELE TIKISA የሚያበቃበት 01/06/2015ዓም' የሚል ጽሑፍ ምስል

ዮሰን በቀለ ትክሳ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ አስተዳደር ቡራዩ ክፍለ ከተማ

ሐሰተኛ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎትን መታወቂያ ይዘው ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

የሌሎች መንግሥታዊ ተቋማትንም ሐሰተኛ መታወቂያ በመጠቀም ለሕገ-ወጥ ድርጊት የሚያውሉ ግለሰቦች በጸጥታ አካላት የተቀናጀ ሥምሪት መያዛቸውን መረጃው ያመለክታል።

የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱንና የሌሎችን ተቋማት መታወቂያ አስመስለው በማሠራት የሚጠቀሙ ግለሰቦች መንግሥት የጀመረውን የጸረ ሙስና ትግል ተከትሎ የሚወስዳቸውን እርምጃዎች ጭምር ለማደናቀፍ ያለሙ መሆናቸውን መረጃው ጠቁሟል፡፡

ኅብረተሰቡ የመንግሥታዊ ተቋማት አባል ነን በማለት በሐሰተኛ መታወቂያ የማጭበርበር ድርጊት ለመፈጸም ከሚሞክሩ ግለሰቦች ጋር በተያያዘ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙት በ910 ነፃ የስልክ መስመርና Info@niss.gov.et በሚለው የኢሜይል አድራሻ ለብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት እንዲሁም በ816 እና 987 ነፃ የስልክ መስመር ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ጥቆማ መስጠት እንደሚችል ከአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም