የኢትዮጵያ አየር መንገድ “በ2022 ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ዘርፍ” ቀዳሚ በመሆን ተሸለመ - ኢዜአ አማርኛ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ “በ2022 ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ዘርፍ” ቀዳሚ በመሆን ተሸለመ
114
አዲስ አበባ (ኢዜአ) ታህሳስ 4/2015 የኢትዮጵያ አየር መንገድ በግሎባል ትራቭለር መጽሔት “በ2022 ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ ዘርፍ” ቀዳሚ በመሆን ተሸለመ።
የአሜሪካው “Global Traveler” መፅሔት ከመንገደኞች በሚያሰባስበው ድምፅ የተለያዩ እውቅናዎችን ሰጥቷል።
በዚህም መሠረት በሚያበረክተው የእውቅና ሽልማት የኢትዮጵያ አየር መንገድ “የ2022 ዓ.ም ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ” ዘርፍ አሸናፊ ሆኗል።
በዘርፉ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ቀጥሎ ሮያል ኤይር ሞሮኮ፣ ኬኒያ ኤይር ዌይስ፣ኤይር ሲሼልስ እና ኤይር ሞሪሽየስ በቅደም ተከተል ከሁለት እስከ አምስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል።