የማይጨው ከተማ የኤሌክትሪክ አገልግሎት አገኘች - ኢዜአ አማርኛ
የማይጨው ከተማ የኤሌክትሪክ አገልግሎት አገኘች
113
አዲስ አበባ (ኢዜአ) ህዳር 30/2015 የማይጨው ከተማ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማግኘቷን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።
አካባቢው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳግም ያገኘው ከአላማጣ-ማይጨው የተዘረጋው የ66 ኪሎ ቮልት የሃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና ተከናውኖ በመጠናቀቁ ነው።
በቀጣይ ሌሎች ኤሌክትሪክ የተቋረጠባቸው አካባቢዎች መልሰው እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።