17ኛዉ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በአፋር ክልል ደረጃ በሰመራ ከተማ አየተከበረ ነው

200

ሰመራ (ኢዜአ)ህዳር 21/2015....17ኛዉ የብሄር ብሄሰሰቦች ቀን በአፋር በክልል ደረጃ በሰመራ ከተማ አየተከበረ ይገኛል፡፡

በአሉ ላይም የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባና የክልሉ ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ አስያ ከማል እንዲሁም የአማራና ደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች ተገኝተዋል፡፡

በተጨማሪም ከአጎራባች አማራ ክልል ደቡብና ሰሜን ወሎ ፣ ከኦሮሚያ ልዩ ዞን አመራሮች ፣ ከአፋር ክልል የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡

በዓሉ እየተከበረ ያለው በፓናል ውይይት ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም