የኬኒያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ አዲስ አበባ ገቡ

150

አዲስ አበባ መስከረም 26 / 2015 (ኢዜአ) የኬኒያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ።

ፕሬዚዳንቱ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

May be an image of 14 people

በአቀባበል ሥነስርዓቱ ላይ የአገር መከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ እና የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

May be an image of 7 people, people standing and outdoors

ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በሚኖራቸው የስራ ቆይታ የሁለቱን አገራት ትብብር እና ቀጠናዊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ኢትዮጵያ እና ኬኒያ ጋር ለረዥም ጊዜ የዘለቀ ወዳጅነት እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረት ትብብር ያላቸው አገራት ናቸው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም