የትግራይ ክልል ተወላጆች አሸባሪውን ህወሃት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ከአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት አካሄዱ - ኢዜአ አማርኛ
የትግራይ ክልል ተወላጆች አሸባሪውን ህወሃት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ከአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት አካሄዱ
263
መስከረም 24 /2015 (ኢዜአ) በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች አሸባሪውን ህወሃት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ከአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት አካሄዱ።
ሰልፈኞቹ ባነገቡትና ባሰሙት መፈክር እንደገለጹት አሸባሪው ህወሃት ከህዝብ ፍላጎት በተቃራኒ ለሽብር ዓላማ የቆመ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አሸባሪው ህወሃት ለ3ተኛ ጊዜ የከፈተውን ጦርነት እንዲያቆም አለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫና እንዲያደርግበት ጠይቀዋል።
ህወሃት የትግራይ ህጻናትንና ሴቶችን በጦርነት መማገዱን ሊያቆም ይገባል ብለዋል።
አሜሪካና ሌሎች ምእራባዊያን የሽብር ቡድኑ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ ሊያሳስቡ እንደሚገባም ገልጸዋል።
ሰልፈኞቹ በቀጣይም በእንግሊዝና በእስራኤል ኤምባሲዎች በር ላይ ድምጻቸውን ያሰማሉ ተብሎ ይጠበቃል።