“የሆራ-ሀርሰዴ” ኢሬቻ ባህላዊ ሥርዓቱን ጠብቆ በመከበር ላይ ነው

289

መስከረም 22/2015 (ኢዜአ) በቢሾፍቱ ከተማ እየተከበረ የሚገኘው “የሆራ-ሀርሰዴ” ኢሬቻ በዓል ባህላዊ ሥርዓቱን ጠብቆ በመከበር ላይ ነው።

የበዓል ተሳታፊዎች በዓሉ ወደሚከበርበት ስፋራ በመሄድ የያዙትን ለምለም ሳር በሆራ-ሀርሰዲ ሀይቅ በመንከር ባህላዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ የክረምቱን ጨለማ ዘመን አሳልፎ ወደ ብርሀን ላሸጋገረ ፈጣሪ ምስጋና እያቀረቡ ይገኛሉ።

May be an image of 1 person, standing and outdoors

በዓሉ በአንድነት፣ በመከባበርና በፍቅር በሀይቁ ዳርቻ ከጥዋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ በድምቀት እየተከበረ ነው።

ከኦሮሚያ ክልል እና ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በዓሉን ለመታደም የመጡ እንግዶች በዓሉ ወደሚከበርበት “የሆራ-ሀርሰዴ ሀይቅ” ሲያቀኑ በባህላዊ አልባሳት ተውበው ህብረ ዜማና ጭፈራ ታጅበው እየተጓዙ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም