በድንገተኛ እሳት አደጋ ቤታቸው የተቃጠለባቸው የዘጠኝ አቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤት እድሳት ተጠናቆ በዛሬው እለት ለነዋሪዎቹ ተላለፉ - ኢዜአ አማርኛ
በድንገተኛ እሳት አደጋ ቤታቸው የተቃጠለባቸው የዘጠኝ አቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤት እድሳት ተጠናቆ በዛሬው እለት ለነዋሪዎቹ ተላለፉ
120
መስከረም 15 /2015 (ኢዜአ)በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በድንገተኛ እሳት አደጋ ቤታቸው የተቃጠለባቸው የዘጠኝ አቅመ ደካማ ወገኖች የመኖሪያ ቤት እድሳት ተጠናቆ በዛሬው እለት ለነዋሪዎቹ ተላለፉ።
የቤቶቹ እድሳቱም የተከናወነው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ፅህፈት ቤት ከኤምሲጂ ኮንስትራክሽን ጋር በመተባበር መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የመኖሪያ ቤቱን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ በመገኘት ለነዋሪዎቹ አስረክበዋል።
ከተማ አስተዳደሩ በመዲናዋ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ አጠናክሮ ይሰራል ብለዋል።
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በ2013 ዓመተ ምህረት በድንገተኛ እሳት የመኖሪያ ቤቶቹ ቃጠሎ እንደደረሰባቸው ያገኘነው መረጃ ያሳያል።