ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ መርሃ ግብር አስጀመሩ - ኢዜአ አማርኛ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ መርሃ ግብር አስጀመሩ
94
አዲስ አበባ ሰኔ 24/2014 /ኢዜአ/ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ መርሃ ግብር አስጀመሩ ።
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ወረዳ 2 ሃምሌ 19 አከባቢ የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ መርሃ ግብር ጀመረ ።
የቤት እደሳ መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ናቸው ።
በዚሁ ወቅት እንዳሉትም በአስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎችን ህይወት ማሻሻል የመንግስት ዋነኛው ትኩረት ነው ብለዋል።
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርም በመጀመሪያው ዙር በጉለሌ ክፍለ ከተማ 12 ቤቶችን እንደሚያድስም ተገልጿል።
ለዚህም 5 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር መመደቡም ተገልጿል።
የቤት ዕድሳት የተጀመረላቸው ነዋሪዎችም የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።