የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሰራዊት አባላት እና ሲቪል ሰራተኞች የሽልማትና የእውቅና አሰጣጥ መረሃ-ግብር እየተካሄደ ነው - ኢዜአ አማርኛ
የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሰራዊት አባላት እና ሲቪል ሰራተኞች የሽልማትና የእውቅና አሰጣጥ መረሃ-ግብር እየተካሄደ ነው
50
መጋቢት 13 ቀን 2014 (ኢዜአ) በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የጤና ዋና መምሪያ በህግ ማስከበርና የህልውና እና በዘመቻ ህብረብሔራዊ አንድነት ወቅት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የሰራዊት አባላት፣ሲቪል ሰራተኞች የሽልማትና የእውቅና አሰጣጥ መረሃ-ግብር እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በመረሃ-ግብሩ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላን ጨምሮ የመከላከያ የጤና ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጀነራል ጥጋቡ ይልማ፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ከፍተኛ ጀነራል መኮንኖች፣ ከፍተኛ መኮንኖች በክብር እንግድነት ተገኝተዋል።