ከንቲባ አዳነች አቤቤ የለቡ ሁዋጂያን ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎበኙ - ኢዜአ አማርኛ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የለቡ ሁዋጂያን ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎበኙ
60
መጋቢት 13 ቀን 2014 (ኢዜአ)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የለቡ ሁዋጂያን ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎበኙ::
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ኢንዱስትሪ ፓርኮች በስራ ዕድል ፈጠራና ውጭ ምንዛሬ የሚጠበቀውን ውጤት እንዲያመጡ መንግስት አስፈላጊውን እገዛ ያደርጋል::
በተለይም ፓርኮቹ ምን አይነት ችግሮች እየገጠማቸው ነው ፣እንዴት ሊፈታ ይችላል፣ ከመንግሥት ምን ይጠበቃል የሚለው እየተለየ መሆኑን ተናግረዋል::
የዚህ ጉብኝት ዋና ዓላማም ተግባራዊ ምላሽ ለመስጠት መሆኑንም ከንቲባ አዳነች አብራርተዋል::
በጉብኝቱ ላይ ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይን ጨምሮ የመዲናይቱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል::