የሀገር መከላከያ ሠራዊት የምሥራቅ አናብስቶች የሜዳይና የእውቅና ሽልማት አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ነው - ኢዜአ አማርኛ
የሀገር መከላከያ ሠራዊት የምሥራቅ አናብስቶች የሜዳይና የእውቅና ሽልማት አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ነው
86
ሠመራ፤የካቲት 19/2014 (ኢዜአ) የሀገር መከላከያ ሠራዊት የምሥራቅ አናብስቶች የሜዳይና የእውቅና ሽልማት አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት በአፋር ክልል ሠመራ ከተማ እየተከናወነ ነው።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ በህልውና ዘመቻው ላይ የላቀ ግዳጅ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የሠራዊቱ አባላት የሽልማትና እውቅና እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
የኢፌዲሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ-ማርሻል ብርሃኑ ጁላና ምክትል ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል አበባው ታደሰ እንዲሁም የምሥራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል መሐመድ ተሰማ ፣የአፋር ክልል ከፍተኛ አመራሮች ፣ የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃርና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።
የተሸላሚ ቤተሰቦች ፣ የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎች እንግዶች መታድመዋል።