ግምቱ 2 ሚሊየን ብር የሚጠጋ የኮንትሮባንድ እቃ ተያዘ

43

ጥቅምት 04 ቀን 2014 (ኢዜአ) በምስራቅ ሐረርጌ ኮምቦልቻ ወረዳ ግምቱ 2 ሚሊየን ብር የሚጠጋ የኮንትሮባንድ እቃ መያዙን ፖሊስ አስታወቀ።

የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ዲቪዥን ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ቶሎሳ ጎሹ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኮንትሮባንድ እቃዎቹ የተያዙት ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት ትናንት ሌሊት አንድ ግለሰብ በተከራየው መጋዘን ውስጥ ነው።

በፖሊስ ከተያዙት ዕቃዎች መካከል የተለያዩ ሲጋራዎች፣ የመኪና ጎማዎች፣ የዝናብ ላስቲክ ሸራዎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።የመጋዘኑ ባለቤትም ሆነ ተከራዩ ግለሰብ ለጊዜው ከአካባቢው መሰወራቸውንና ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑን ዋና ኢንስፔክተር ቶሎሳ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም