የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አየር ወለድና ኮማንዶ አያስመረቀ ነው

150

መጋቢት 18/2013 (ኢዜአ) ብላቴ መጋቢት 18/2013 (ኢዜአ) የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የ12ኛ ዙር አየር ወለድ ብርጌድና የ34ኛ ዙር ኮማንዶ አያስመረቀ ነው።

ተመራቂዎቹ ብላቴ በሚገኘው የልዩ ዘመቻዎች ሃይል ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠናቸውን የተከታተሉ ናቸው።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሰራዊት ግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጀነራል ባጫ ደበሌ ፣የልዩ ዘመቻዎች ሀይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሹማ አብደታ እና የሪፐብሊካን ጋርድ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ብርሀኑ በቀለ ተገኝተዋል

ተመራቂዎቹ በአሁኑ ወቅት በስልጠና ቆይታቸው ያገኙትን ትምህርት በተግባር የተደገፈ ትርኢት እያሳዩ ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም