የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በድሬዳዋ ተጀመረ - ኢዜአ አማርኛ
የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በድሬዳዋ ተጀመረ
79
ድሬዳዋ ጥር 16 /2013 (ኢዜአ) 8ተኛው የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፕሪሚየር ሊግ 1ኛ ዙር የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ዛሬ በድሬዳዋ ተጀመረ ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሻኪር አህመድ ውድድሩን አስጀምረዋል ።
ከዛሬ ጥር 16 እስከ 22 ቀን 2013 ዓም በሚቆየው ውድድር አምስት የወንድና አምስት የሴት ክለቦች ይሳተፋሉ።
በአማራ መንገድና ህንጻ ዲዛይንና በሀዋሳ ከተማ ሴቶች ቡድን መካከል በሚደረግ ጨዋታ የመክፈቻ ውድድሩ ተጀምሯል ።
የጅማና ወልቂጤ ከተማ የሴት ቡድኖ እንዲሁም በወንዶች ወልቂጤ ከሀዋሳ ከተማና ድሬዳዋ ከጎንደር ከተማ በዛሬው እለት እንደሚጫወቱ ታውቋል ።