ፋሲል ከነማ በቱኒዚያው ዩኤስ ሞናስቲር ተሸንፏል - ኢዜአ አማርኛ
ፋሲል ከነማ በቱኒዚያው ዩኤስ ሞናስቲር ተሸንፏል
64
አዲስ አበባ፣ ህዳር 19/2013 (ኢዜአ) በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ እግር ኳስ ጨዋታ ፋሲል ከነማ / አፄዎቹ/ በቱኒዚያው ዩኤስ ሞናስቲር በሁለት ለዜሮ ውጤት ሽንፈትን አስተናግደዋል።
ፋሲል ከነማ እ.አ.አ በ2020/2021 በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ የእግር ኳስ ጨዋታ ኢትዮጵያን ወክሎ እየተሳተፈ ነው።
ትናንት ምሽት የመጀመሪያ ዙር የማጣሪያ ጨዋታውን ከሜዳው ውጭ ከቱኒዚያው ዩኤስ ሞናስቲር ጋር ያደረገው ፋሲል ከነማ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።
አፄዎቹ የመልስ ጨዋታቸውን ከዩኤስ ሞናስቲር ጋር በሚቀጥለው ሣምንት የሚያካሂዱ ይሆናል።
በሁለቱ ክለቦች የደርሶ መልስ ጨዋታ አሸናፊው ክለብ ከሊቢያው አል-አህሊ ትሪፖሊን ጋር ይጫወታል።