ፓርቲዎች በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ነው - ኢዜአ አማርኛ
ፓርቲዎች በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ነው
58
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5/2013(ኢዜአ) በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ነው።
በውይይቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በተሳታፊነት ተገኝተዋል።
ፓርቲዎቹ በመወያየት ላይ ያሉት ህገ-መንግስትና ህገ-መንግስታዊነት በኢትዮጵያ፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አደረጃጀት ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው፣ ዴሞክራሲያዊ ምርጫና የማያግባቡን ታላላቅ አጀንዳዎች በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው።
እስካሁን ባለው ህገ-መንግስትና ህገ-መንግስታዊነት በኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ፖለቲካ አደረጃጀት ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው በሚሉት አጀንዳዎች ላይ የመወያያ ጽሁፎች ቀርበዋል።
በቀሪ አጀንዳዎች ላይም ለውይይቱ መነሻ የሚሆኑ ጽሁፎች ቀርበው ፓርቲዎቹ ይመክሩባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።