ፌስቡክ በናይጀሪያ ዋና ከተማ ቢሮውን ሊከፍት ነው - ኢዜአ አማርኛ
ፌስቡክ በናይጀሪያ ዋና ከተማ ቢሮውን ሊከፍት ነው
94
መስከረም 10/2013(ኢዜአ) ግዙፉ የፌስቡክ ካምፓኒ በሚቀጥለው የፈረንጆች አመት በናይጀሪያ ዋና ከተማ ሎጎስ ቢሮውን ሊከፍት መሆኑን አስታውቋል።
ይህውም ካምፓኒው በአፍሪካ አህጉር ጽ/ቤቱን ሲከፍት ለሁለተኛ ጊዜ ያደርገዋል ተብሏል።
እንደ ኩባንያው መረጃ ከሆነ ይህ ጽ/ቤት የመሐንዲሶችን ቡድን የሚያስተናግድ የመጀመሪያው የአፍሪካ ቢሮ ይሆናል።
በናይጄሪያ የሚከፈተው ቢሮ በሽያጭ ፣ በሽርክና ፣ በፖሊሲ እና በኮሙኒኬሽን ውስጥ የሚሰሩ ቡድኖችን ያካትታል መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ፌስቡክ በሰጠው መግለጫ አዲሱ ማዕከል በአፍሪካውያን የተፈጠሩ ምርቶችን ለአፍሪካና ለመላው ዓለም ያዳርሳል የሚል እምነት አለኝ ብሏል።
እ.አ.አ በ 2016 የኩባንያው መስራች የሆኑት ማርክ ዙከርበርግ ወደ አፍሪካ አህጉር ባደረጉት የመጀመሪያ ጉዞው ሌጎስን መጎብኘታቸው የሚታወስ ነው።